የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡
(መስከረም 5/2018 ዓ.ም) የ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች የሚያገኙበት አድራሻዎችም ይፋ ተደርጓል፡፡
ዌብ ሳይትና ቴሌግራም አድራሻ የሚጠቀሙ ተፈታኞች ጊዜያዊ ሰርቲፊኬታቸውን ወዲያውኑ አውርደው (download አድርገው) መውሰድና መጠቀም ይችላሉ፡፡
ተብሏል::
ውጤት ለመመልከት አድራሻዎች:-
1. በዌብ ሳይት፡ https://result.eaes.et
2. በቴሌገራም፡ https://t.me/EAESbot
3. በአጭር የጽሑፍ መልዕክት (SMS)፡ 6284 ላይ ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ አድርጓል::