Karalo Secondary School
Announcement በ2016 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ተፈትነው ወደዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት 46

በ2016 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ተፈትነው ወደዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት 46

08th October, 2024

                የካራአሎ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት 

የካራአሎ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት በ2016 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ተፈትነው ወደዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ ያስመዘገቡ ተማሪዎች ብዛት 46 ሲሆን ካሉት የመንግስት 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች በክፍለ ከተማ ደረጃ 3ኛ እንዲሁም ከ500 በላይ ያስመዘገቡ 2 ተማሪዎች በብቸኝነት የካራአሎ ት/ቤት ነው፡፡ ሁለቱ ተማሪዎች በከተማ ደረጃ እንዲሁም በክፍለ ከተማ ደረጃ መስከረም 27/2017 ዓ.ም በተካሄደ የዕውቅናና ሽልማት ፕሮግራም የግብዓትና ገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ለዚህ ውጤት መሳካት ጉልህ ሚና ለነበራችሁ ባለቤት ለሆናችሁ ተማሪዎች፣ አጠቃላይ በይበልጥም በተለያየ መንግድ ተማሪዎችን ስትደግፉ የነበራችሁ የ12ኛ ክፍል መ/ራን፣ ወተመህ አባላት የማጠናከሪያ ትምህርት እንዲሰጥ ላበረከታችሁ ድጋፍ፣ ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች፣ አስተዳደር፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ በአጠቃላይ ለዉጤቱ መሳካት አሻራችሁን ላሳረፋችሁ ሁሉ በት/ቤቱ ስም ላቅ ያለ ምስጋና እያቀረብን በ2017 ትምህርት ዘመንም ይህንን መነሻ በማድረግ በየደረጃው ያላችሁ ባለድርሻ አካላት ከዚህ በበለጠ ድጋፍና ክትትል በማድረግ በሁሉም የክፍል ደረጃ ጭምር የተማሪዎች ስነ ምግባርና ውጤት በማሻሻል የት/ቤቱ ገፅታ ወደተሻለ ደረጃ እንደምናሳድግ በመተማመን ለነበረው ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ!!!
.

Copyright © All rights reserved.

Created with